የሚገርም ታማኝነት ይህ ሶርያዊ ስደተኛ በቱርክ ውስጥ ነው የሚኖአው። በቅርቡ በቱርክ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት በፈራረሰው ህንፃ ስር በቦርሳ የታጨቀ 75ሺ $ ዶላር ያገኛል። ታድያ ይህንን ሶርያዊ የዶላሩ ብዛትና የሱ ችግር ታማኝነቱን እንዲያጎልና የሰውን ሀቅ እንዲበላ አላደረገውም። ዶላሩን እንዳገኘ ያለምንም ማንገራገር ቀጥታ የብሩን ባለቤቶች ልያገኙለት ወደሚችሉ ፖሊሶች ነበር ያመራው። ፖሊሶቹም ስራቸውን ሰሩ። የገንዘቡ ባለቤትም ተገኘ። ርክክቡንም በመፈፀም ዱዓ ተደረገለት። አጂብ ነው። አለም ቀማኛ በሆነችበት ዘመን እንዲህ ያሉ ታማኞች መኖራቸው ያስገርማል። 1.0K viewsMotivational Speaker, 19:56