Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 130.32K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-14 11:19:39
አቶ አብነት ገብረመስቀል በቦሌ ታወርስ ላይ ያላቸውን ድርሻ ለቀው እንዲወጡ ተፈረደባቸው!

አቶ አብነት በነሃሴ 2014 ዓም አቅርበውት በነበረው ክስ የቀድሞ የቅርብ ወዳጃቸው እና አጋራቸው የሆኑት ሼክ መሃመድ ሁሴን አሊ አልአሙዲ በቦሌ ታወር ያላቸውን ድርሻ ለቀው እንዲወጡ ወይም ድርጅቱ እንዲፈርስ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም፡፡

ባሳለፍነው ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 የዋለው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የንግድ እና ኢንቨስትመንት ችሎት በሰጠው ውሳኔ ቦሌ ታወርስ የተባለው እና በወሎ ሰፈር አካባቢ የህንጻ ግንባታ ያለው ድርጅት እንዳይፈርስ የወሰነ ሲሆን፡፡
በተጨማሪም አቶ አብነት የሚገባቸው ድርሻ ተከፍሏቸው ከድርጅቱ ለቀው እንዲወጡ ወስኗል፡፡ቢሊየነሩ ሼክ መሃመድ በቦሌ ታወርስ ላይ የ60 በመቶ ድርሻ ያላቸው ሲሆን ቀሪው በቀድሞ አጋራቸው የተያዘ ነው፡፡

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
14.1K views08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 07:06:59
Are you interested in becoming an AI engineer?

Join the Kifiya AI Mastery Training Program (Kifiya AIM 1) by Kifiya Financial Technology and 10 Academy. It's a 3-month intensive course beginning on April 29, 2024, focusing on Machine Learning and Data Engineering. Gain fast career advancement in AI and data science through industry-led projects, expert sessions, and explore fintech career opportunities in Addis Ababa, Ethiopia. Special consideration for women and vulnerable groups.

Eligibility criteria:

- Undergraduates (preferred) aged 22-34

- Has legal right to work in Ethiopia.

- Fluent in English (B1 CEFR level), with some background in Python, SQL, and Statistics.

- Ready to commit 30-40 hours weekly, with a strong work ethic and community spirit.

Submit your application by the deadline of April 17, 2024.

Application link: https://apply.10academy.org/login

Learn more about the program: https://10academy.org/kifiya/learn-more

For any question, contact us at kifiya_ai@10academy.org
14.3K views04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 02:24:38 ኢራን በእስራኤል ላይ የምትሰነዝረውን ጥቃት መጀመሯን አስታወቀች!

ኢራን ወደ እስራኤል በርካታ ቁጥር ያላቸው ድሮኖችን እና ሚሳዔሎችን መተኮሷን አስታወቀች።እስራኤል ባሳለፍነው ሳምንት በሶሪያ መዲና ደማስቆ በሚገኝ የኢራን ኢምባሲ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ሁለት ወታደራዊ አዛዦችን ጨምሮ ዘጠኝ ኢራናዊያ መገደላቸው ይታወሳል።ይህንን ተከትሎ በኢምባሲዋ ላይ ለደረሰው ጥቃት እስራኤልን እንደምትበቀል ስትዝት የቆየችው ኢራን በዛሬው እለት መጠነ ሰፊ የድሮን እና ሚሳዔል ጥቃተ ወደ ቴልአቪቭ መክፈቷን አስታውቃለች።

የኢራን ሪቮሉሽናሪ ጋርድ ዛሬ ምሽት በሰጠው መግለጫው፤ ወደ እስራኤል ድንበር በርካታ ሚሳዔሎችን እና ድሮኖችን መተኮሱን አስታውቋል።እስራኤል በበኩሏ በርካታ ድሮኖች ከኢራን መተኮሳቸውን ያረጋገጠች ሲሆን፤ ሚሳዔል ስለመተኮሱ ግን እስካሁን ማረጋገጫ አላገኘሁም ብላለች።የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ በሰጡት አስተያየት፤ ኢራን ወደ የተኮሰቻቸው ድሮኖች የእስራኤል ድንበር ላይ ለመድረስ ሰዓታት ይፈጃሉ ብለዋል።

ኢራን ወደ እስራኤል ድሮኖችን እና ሚሳዔሎችን እንደተኮሰች ማሳወቋን ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ሁኔታ በፍጥነት እየተቀያየረ ሲሆን፤ መንግስታትም የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛል።ጆርዳን፣ ሊባኖስ እና ኢራቅ የአየር ክልላቸውን መዝጋታቸውን ያስታወቁ ሲሆን፤ እነዚህ ሶስቱ ሀገራት የኢራን ድሮኖች እና ሚሳዔሎች ሊያልፉባቸው የሚችሉ ናቸው ተብሏል።ኢራን እና እስራኤልም ከወታደራዊ አውሮፕላኖች በስተቀር ለሌሎች አውሮፕላኖች የአየር ክልላቸውን መዝጋታቸው ነው እየተነገረ ያለው።

ኢራን በእስራኤል ላይ የአየር ወለድ ጥቃትን መጀመሯን የአሜሪካው ነጩ ቤተ መንግስት ወይም ዋይት ሀውስ አስታውቋል።የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በብሔራዊ ደህንነት ቡድናቸው አማካኝነት ስለሁኔታው በመደበኛነት እየተከታተሉ መሆኑም ተነግሯል።ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና ቡድናቸው ከእስራኤል ባለስልጣናት ጋር በተደጋጋሚ ግንኙነቶችን እያደረጉ እየተወያዩ መሆኑን ዋይት ሃውስ አስታውቋል።አሜሪካ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተጨማሪ ኃይል መላኳም ይታወሳል።

[Al Ain]
@YeneTube @FikerAssefa
13.6K views23:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 23:23:23
ሰላም፣ ቆንጆ ፉድስ ነን!

የኢትዮጲያ ባህላዊ ምግቦች በሚገባቸው ክብር እና ደረጃ በማቀናበር ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ቆርጠን ተነስተናል። እርስዎም ይህንን መጠይቅ በመሙላት የሚወዷቸውን ኢትዮጲያዊ ጣዕሞችን በመላው በዓለም ያገኟቸው ዘንድ የበኩልዎን አስተዋፅዎ እንዲወጡ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

ለሚያደርጉት አስተዋፅዎ ያዘጋጀነውን የምስጋና ሽልማት ለመቀበል ስልክ ቁጥሮን መተው እዳይረሱ፣ እናመሰግናለን።

የሚከተለውን ሊንክ በመጫን ወደ ፎርሙ ይግቡ
https://forms.gle/dZ9qwg2L3bJsX9NR7
12.7K views20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 20:50:00
በዛሬው ዕለት ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ!

በ3ኛው ምዕራፍ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በሳኡዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለስ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለትም በሶስት ዙር በረራ 1 ሺህ 71 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል።

በዛሬው እለት ወደ ሀገር የተመለሱት 1 ሺህ 71 ዜጎች ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ ዘጠኙ እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ናቸው ተብሏል።

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
14.0K views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 20:48:31
ለድርጅትዎ የGOOGLE ማስታወቂያ ማሰራት ይፈልጋሉ?

ማስታወቂያዎት ደንበኛ ሊሆንዎት ከፍተኛ እድል ወዳላቸው ሰዎች(Potential
Customers) እንዲደርስስ?

-ጉግል ሰርች ላይ ለሚመጡ ማስታወቂያዎች፤
-በዩቲውብና ጂሜይል ለሚታዩ ማስታወቂያዎች፤
-በተለያዩ አፕሊኬሽኖች ላይ የሚታዩ ማስታወቂያዎችን በማሰራት ምርትና አገልግሎትዎን ለማሳደግ ከፈለጉ ያናግሩን።

ከዚህም በተጨማሪ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ኤክስን በመሳሰሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ማስታወቂያ ማሰራትም ይችላሉ።

ቴሌግራም፡ @adsommar
ስልክ፡ 0954260423
13.1K views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 18:01:13
ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ውጥረት ለማርገብ ኬንያ ያቀረበችው የባሕር ጠረፍ ስምምነት ሃሳብ የለም አለች!

ኬንያ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያን ውጥረት ለማርገብ ቀጣናዊ የባሕር ጠረፍ አገልግሎት ስምምነት አማራጭ ለአገራቱ አቅርቤያለሁ ማለቷን ሶማሊያ ውድቅ አደረገች።

ኬንያ አቀረብኩት ያለችው አማራጭ በቀጠናው የሚገኙ የባሕር በር የሌላቸው አገራት በንግድ ስምምነት መሠረት የባሕር መተላለፊያ አገልግሎት እና ጥቅም የሚያገኙበትን ዕድል የሚፈጥር ነው ተብሎ ነበር።የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ ከኬንያ በኩል የተባለው ዓይነት የቀረበ ስምምነት የለም ብሏል።

የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲዔታ ዓሊ ኦማር ባላድ “ሶማሊያ እና ኢትዮጵያን የሚመለከቱ የባሕር ጠፈር ስምምነት ዘገባዎች ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ ናቸው” ሲሉ ሚያዝያ 4/2016 ዓ.ም በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።አክለውም “ሶማሊያ በግዛት አንድነቷ ላይ እንደማትደራደር” ጠቅሰው “በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ትኩረት እንዲደረግ” ጠይቀዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
13.4K views15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 15:57:35
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የአገልግሎት ክፍያ ተመን ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ!

ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የነበረዉን ደንብ በመሻር የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ለሚሰጣቸው የአገልግሎት ክፍያ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታዉቋል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አዲሱ ደንብ ከመዉጣቱ በፊት ሲሰራበት የነበረዉን የሰነዶች ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያን በመሻር ማሻሻያዉ ከሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ለሚሰጣቸው የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያ ለመወሰን ባወጣዉ በዚህ ደንብ በተቀመጠው አዲሱ የክፍያ መጠን የሰነድ አይነቶቹ ቢለያይም ለሁሉም አገልግሎቶች ከ 200 ብር ጀምሮ እስከ 500 ብር ድረስ ክፍያን ይጠይቃል።

ካፒታል በተመለከተዉ በዚህ ደንብ ላይ ለሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዉል ሰነድ ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረቶች ሽያጭ ፣ ለመመስረቻ ፅሁፍ ሰነድ እና በስጦታ መልክ ለሚሰጡ ንብረቶች ዉል ሰነድ የክፍያ አገልግሎት ተመን ከወጣላቸው መካከል ዉስጥ ተካተዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
13.6K views12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 11:26:32 ከኢትዮጵያ ለመጡ ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ የከለላ ፈቃድ ተራዘመ!

ለተለያዩ ጉዳዮች መጥተው አሜሪካ ውስጥ የሚገኙ የኢትዮጵያ ዜጎች፣ በሀገራቸው ባለው የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት ካለፈው ጥቅምት 10/2015 ዓ.ም. ጀምሮ ለ18 ወራት ተሰጥቶ የነበረው የከለላ ፈቃድ ወይም ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ እንዲቆዩ የሚፈቅደው ደንብ፣ ለሌላ 18 ወራት መራዘሙን የአሜሪካው የሀገር ውስጥ ደህነት ሚኒስትር አሌሃንድሮ ማዮርካስ ዛሬ አስታውቀዋል።

አዲስ የተራዘመው የከለላ ፈቃድ ከሐሙስ ሰኔ 6፣ 2016 እስከ ታኅሣሥ 3፣ 2018 ተግባራዊ እንደሚደረግ ከሃገር ውስጥ ደህነት ሚኒስቴሩ ዛሬ ዓርብ ሚያዚያ 4፣ 2016 የወጣው መግለጫ አመልክቷል።“በሃገሪቱ የሚካሄደው የትጥቅ ግጭት እንዲሁም ለየት ያሉ ጊዜያዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች፣ ግለሰቦች ደህንነታቸው በተጠበቀ ሁኔታ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ ስለማያስችሉ፣ የከለላው መራዘም አስፈላጊ ሆኗል” ሲል መግለጫው ጨምሮ ገልጿል።

“በኢትዮጵያ የትጥቅ ግጭቱ እና ሁከቱ በበርካታ ክልሎች ቀጥሏል፣ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ተበራክተዋል፣ ሲቪሎች ለጥቃት ተጋልጠዋል። ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋ እና የበሽታ ወረርሽኝ የሚሊዮኖችን ሕይወት አደጋ ላይ ጥሏል” ሲል አክሏል። በመሆኑም የከለላው መራዘም አስፈላጊ እንደሆነ አመልክቷል። ሚኒስትሩ አሌሃንድሮ ማዮርካስ ከተለያዩ ሌሎች መ/ቤቶች ጋራ በመመካከር ከለላው ለ18 ወራት እንዲራዘም መወሰናቸው ተመልክቷል።

በከለላው ተጠቃሚ ለመሆን የሚሹ ኢትዮጵያን የሚመዘገቡበትን ድህረ ገጽም ሚኒስቴር መ/ቤቱ ይፋ አድርጓል።ከከለላው መራዘም ጋራ ተያይዞ የወጣውና F–1 በሚል ቪዛ ወደ አሜሪካ የመጡ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን የሚመለከተው መግለጫ እንደሚያሳየው፣ የኢትዮጵያ ዜግነት ያላቸውና በአሜሪካ የሚገኙ ተማሪዎች፣ ከለላው በተራዘመበት የግዜ ገደብ ውስጥ፤ የሥራ ፈቃድ መጠየቅ እንዲችሉ፣ ተጨማሪ ሠዓታት እንዲሠሩ እንዲሁም የሚወስዱትን የትምህርት ኮርሶች መጠን መቀነስ እንዲችሉ ይፈቅዳል።

“ጊዜያዊ የከለላ ፈቃድ፤ በአሜሪካ የሚገኙ ግለሰቦች፣ በሃገራቸው ያለው ሁኔታ፣ ደህነታቸው በተጠበቀ መንገድ እንዲመለሱ በማያስችል ጊዜ ከለላ ይሰጣቸዋል” ሲሉ ሚኒስትሩ ማዮርካስ መናገራቸው በመግለጫው ተመልክቷል። ከትናንት ሚያዚያ 3፣ 2016 በፊት አሜሪካ የገቡ ኢትዮጵያን የገጠማቸው ሁኔታም ይኽው እንደሆነ የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ “ለጊዜው ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ሰብአዊ እፎይታ የመሰለ ከለላ ሰጥተናቸዋል” ብለዋል።

ከተመዘገቡ እና ከለላው የሚጠይቀውን መሥፈርት ካሟሉ፣ ከዚህ ቀደም የወጣው ከለላ ተጠቃሚ የሆኑ 2ሺሕ 300 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን እስከ ታኅሣሥ 3፣ 2018 ድረስ የከለላው ተጠቃሚነታቸው እንደሚራዘምላቸው ተመልክቷል።ኢትዮጵያን አስመልክቶ የተራዘመው የከለላ ደንብ፣ 12ሺህ 800 የሚሆኑና ከትናንት ሚያዚያ 3፣ 2016 በፊት አሜሪካ እንደገቡና በሃገሪቱ መቆየታቸውን ማረጋገጥ የሚችሉ ኢትዮጵያውያን፣ ወይም መኖሪያቸውን ኢትዮጵያ አድርገው የነበሩ ሌሎች ግለሰቦች፣ ተጠቃሚ ሊያደርግ እንደሚችል ታውቋል።

ኢትዮጵያውያን፣ ወይም መኖሪያቸውን ኢትዮጵያ አድርገው የነበሩ ሌሎች ግለሰቦች፣ አሜሪካ የገቡት ከትናንት ሚያዚያ 3፣ 2016 በኋላ ከሆነ፣ ከለላው እንደማይመለከታቸው የሃገር ውስጥ ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስታውቋል።

እንደገና ከለላ ለማገኘት መመዝገብ የሚችሉትም፣ ከዚህ በፊት በመጀመሪያ ኢትዮጵያን አስመልክቶ ወጥቶ በነበረው የከለላ ደንብ ተመዝግበው የነበሩት ብቻ መሆናቸው ተገልጿል።በአሁኑ ወቅት የከለላው ተጠቃሚ የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ ከለላቸውንም ሆነ የሥራ ፈቃዳቸውን ይዘው ለመቆየት፣ ለምዝገባ በተፈቀደው 60 ቀናት ውስጥ፣ ማለትም ከሚያዚያ 7፣ 2016 እስከ ሰኔ 7፣ 2016 ድረስ እንዲመዘገቡ ሚኒስቴር መ/ቤቱ አሳስቧል።

ከዚህ በፊት በወጣው ከለላ መሠረት ለከለላውም ሆነ ለሥራ ፈቃድ እስከ ሚያዚያ 7፣ 2016 ድረስ ያመለከቱ ወይም የሚያመለክቱ ግለሰቦች፣ ለሁለቱም ጉዳዮች እንደገና ማመልክት እንደማያስፈልጋቸው መ/ቤቱ አስታውቋል። የአሜሪካ የዜግነትና የፍልሰተኞች አገልግሎት (USCIS) ከዚህ በፊት የተቀበላቸውን ማመልከቻዎች እየተመለከተና ውሳኔ እየሰጠበት መሆኑም ተመልክቷል። ከዚህ በፊት በወጣው ከለላ መሠረት የገባን ማመልከቻ፣ የአሜሪካ የዜግነትና የፍልሰተኞች አገልግሎት (USCIS) የሚያጸድቀው ከሆነ፣ ከለላውም ሆነ የሥራ ፈቃዱ እስከ ታኅሣሥ 3፣ 2018 እንደሚሰጥ ታውቋል።በአዲሱ የከለላ ፈቃድ መሠረት ለከለላም ሆነ ለሥራ ፈቃድ ማመልከት የሚሹ፣ ከሚያዚያ 7፣2016 እስከ ታህሳስ 3፣ 2018 መመዝገብ እንደሚችሉ ታውቋል።

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
14.1K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 10:17:38
ኢትዮ ጂቡቲ ባቡር የአገልግሎት የግንባታ ማሽኖችን ለመጀመሪያ ጊዜ ማጓጓዙን አስታወቀ!

ድርጅቱ እንዳስታወቀው ከጅቡቲ ናጋድ ባቡር ጣቢያ ተጭነው እንዶዴ የባቡር ጣቢያ የደረሱ አምስት ኤክስካቫተሮችን በትላንትናው እለት ለደንበኞች አስረክቧል፡፡

መሰል ጭነት በኢትዮ ጅቡቲ የባቡር አገልግሎት ሲጓጓዝ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን ያስታወቀው ድርጅቱ በቅርቡ ተጨማሪ የኮንስትራክሽን ግዙፍ ተሽከርካሪዎች ከጂቡቲ ናጋድ ባቡር ጣቢያ ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ ብሏል።

በተመሳሳይ ሌሎች አዳዲስ አገልግሎት እንደሚያስጀምርም ድርጅቱ ቀደም ሲል ለካፒታል ተናግሯል፡፡

@Yenetube @Fikerassefa
13.1K viewsedited  07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ